(ዘ-ሐበሻ) በዲላ ዩኒቨርሲቲ ለ4ኛ ቀን አለመረጋጋቱ እንደቀጠለ ነው:: ከቀናት በፊት ቦምብ መፈንዳቱ እንደዚሁም 3 ተማሪዎች በመጸዳጃ ቤት ውስጥ ታርደው መገኘታቸው በዘ-ሐበሻ መዘገቡ አይዘነጋም::
ዛሬ ከስፍራው ለዘ-ሐበሻ የደረሰው መረጃ እንደሚጠቁመው የዩኒቨርሲቲው የወንዶች ማደሪያ ህንፃ እየተቃጠለ ነው:: የ እሳቱ መነሻ ምን እንደሆነ አልታወቀም::
ይህ ዜና እየተጠናቀረ ባለበት በዚህ ወቅት አካባቢው በተኩስ እየተናወጠ ሲሆን ተማሪዎችም ግቢውን ለቀው እየወጡ እንደሆነ ታውቋል::
Advertisements
Discussion
No comments yet.